የህንፃ ግንባታ ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ በአዲስ አበባ ከተማ ኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ወረዳ 5 ክልል ውስጥ ለሚያስገነባው ባለ 2B+G+7 የፍትህ አካላት ህንፃ ደረጃቸው BC-1 ወይም GC-2 እና ከዚያ በላይ የሆኑ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር የህንፃ ተቋራጮችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ስለዚህ ከዚህ በታች የቀረቡትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተወዳዳሪዎች መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

  1. በስራ ዘርፍ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያለውና የዘመኑን ግብር የከፈለ፡፡
  2. የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢነት የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል፡፡
  3. በመንግስት አቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ መመዝገቡን የሚያረጋግጥ መረጃ ያለው፡፡
  4. የመልካም ስራ አፈፃፀም ማሰረጃ ካለው ማቅረብ የሚችል፡፡
  5. ሌሎች በጨረታ ሰነዱ ላይ የተገለጹ የቴክኒክ መመዘኛዎችን ማሟላት የሚችል፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ የማይመለስ ብር 200.00(ሁለት መቶ ብር) በመክፈል ከሚኒስተር መስሪያ ቤት ቢሮ ቁጥር 002 ጨረታው በጋዜጣ ከመጣበት ቀን ማግስት ጀምሮ መግዛት ይችላሉ
  7. ተጫራቾች የጨረታ ማስረከቢያ ብር 500.000.00(አምስት መቶ ሺህ ብር )በባንክ የተረጋገጠ ቼክ (cpo) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመስረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ አለባቸው፡፡
  8. የግልጽ ጨረታው አሸናፊ ከታወቀ ለጫረታ ማስረከቢያ የተያዘው ገንዘብ ለአሸናፊዎች ወድያውኑ ተመላሽ ይደረጋል፡፡
  9. ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ ሲያቀርቡ የተጨማሪ እሴት ታክስን ያጠቃለለና ከላይ የተጠቀሱትን ማስረጃዎች አሟልተው በታሸገ ኤንቨሎፐ የቴክኒክ እና ዋጋ መወዳደሪያቸውን ዋጋ በተለያዩ ፖስታዎች በአንድ ኦርጅናል እና ሁለት ሁለት ኮፒዎች በማዘጋጀት በፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዋና መ/ቤት ለዚሁ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ እስከ ጫረታው መክፈቻ እለት ከጠዋቱ 4፡00 ሰአት ድረስ ብቻ ማስግባት ይኖርባቸዋል፡፡
  10. ግለጽ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ ለ30 ቀናት አየር ላይ ከዋለ በኋላ በ31ኛው ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከጠዋቱ 4፡00 ሰአት ላይ ታሽጎ በዚሁ እለት ከጠዋቱ 4፡30 ሰአት ላይ ይከፈታል፡፡የጨረታው መክፈቻ ቀን ቅዳሜ፤እሁድ ወይም በበዓላት ቀን ከዋለ በሚቀጥለው የመንግስት የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰአት ይከፈታል፡፡
  11. የግልጽ ጨረታው አሸናፊ በተጫራች መመሪያ በተጠቀሰው መሰረት የጨረታው አሽናፊነት በጽሁፍ እንደተገለጸ ወዲያውኑ አስፈላጊውን የውል ማስረከቢያ ማስያዝ ይኖርበታል፡፡
  12. መስሪያ ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ሆን በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  13. ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 09፤ 08፤ 03 በአካል ወይም በስልክ ቁጥር ፡-011-833-41-56/ 011-827-21-40/ 011-828-29-35 ደውሎ ማብራሪያ ማግኘት ይችላሉ፡፡

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ;